የውጭ ጉዳይና ሉዓላዊነትን በተመለከተ፦
የውጭ ጉዳይና ሉዓላዊነትን በተመለከተ፦
ዓለም ሊካድ በማይችል ሁኔታ ተለዋዋጭ በሆነችበት በዚህ ወቅት፤ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም፣ የውጭ ፖሊሲ እና ሉዓላዊነትን ለማስከበር በስትራቴጂካዊ ራስን መቻል ላይ የተመሠረቱ ሦስት ዋና ዋና መርሆችን እንከተላለን፤ የመጀመሪያው መቋቋም ሲሆን፤ ይህም የውጭ ተጽዕኖዎችን በራስ አቅም ለመቋቋም የሚያስችል ጠንካራ ተቋማዊ አቅምን መገንባት ላይ ያተኩራል። ሁለተኛው መጠቀም ሲሆን፤ ይህም ማንኛውንም የሚያጋጥም ፈተና ወደ ስትራቴጂካዊና መልካም የልማት ዕድል የመቀየር ብቃትን ያካትታል። ሦስተኛው ደግሞ መግራት ሲሆን፤ ይህም ሀገሪቱ የራሷን ብሔራዊ አጀንዳ ቀርጻ ዓለም አቀፋዊ ሁነቶችን በልበ ሙሉነት እንድትጋፈጥና እንድትመራ ያስችላታል። በእነዚህ ሦስት ምሰሶዎች በመመራት በማንኛውም ብሔራዊ ውሳኔያችን ላይ የትኛውንም የውጭ አካል ጣልቃ ገብነት ፍጹም አንፈቅድም።
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.